የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከአማራ ክልል ለተወጣጡ የዳኝነት ና የፍትህ ተቋማት የሁለተኛ ዙር የስልጠና መድረክ አዘጋጅቷል።
በመድረኩ ከዚህ ቀደም ስልጠናውን ያገኙትን ከ60 በላይ ተሳታፊዎች በጥልቀት በማሰልጠን ሰርተፊኬት ተሰጥቷል።
ስልጠናው በዋናነት በሀገራችን የተጀመረው የካፒታል ገበያ ስርዓት ተዓማኒነት እንዲኖረው በተለይ የዳኝነት እና የፍትህ አካላት በካፒታል ገበያ ዙሪያ የሚነሱ ክርክሮችን ለመፍታት ተመሳሳይ የሆነ የህግ አተረጓጎም እንዲኖር ለማስቻል በህግ ማዕቀፉ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡
አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ በቀጣይ ከክልሉ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር ይህ ስልጠና በአማራ ክልል የፍትህ እና የህግ ኢንስቲቲዩት በኩል በቋሚነት የስልጠና ተቋሙ ውስጥ ለሚገቡ ሰልጣኞች እንዲሰጥ ለማድረግ የሚሰራ ሲሆን ይህም የስልጠናውን ተደራሽነት በማስፋት ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስራ ለመስራት ዝግጁ ነው።

