የኢትዮጵያ የከፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክ/ከተማ የአኔ ዲማ ወረዳ ጋር በመተባበር የችግኝ ተከላ አካሄደ፡፡
አስተዳደራዊ ፍርድቤቱ ከወረዳው አመራሮች እና ነዋሪዎች ጋር በመሆን “በጋራ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ ከ300 በላይ የአፕል ችግኞችን ተክለዋል።
የወረዳው አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ የተከሉት ችግኞች ጥቅም ላይ እንዲውሉ የመንከባከብ ስራውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቃል ገብተዋል።
አስተዳደራዊ ፍርድቤቱ ከሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክ/ከተማ የአኔ ዲማ ወረዳ ጋር በቀጣይ በርካታ ስራዎችን በጋራ እንደሚሰሩ ተገልጿል::


