አስተዳደራዉ ፍርድቤቱ በቡራዩ ክ/ከተማ የማነቃቂያ መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክ/ከተማ አኔ ዲማ ወረዳ ለተወጣጡ አመራሮችና ወጣቶች capital market as an investment alternative for young innovators በሚል ርእስ የማነቃቂያ መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የካፒታል ገበያ ምንነት፣ ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ስለሚያበረክተው አስተዋጽኦ ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ያለው ፋይዳ ለወጣት ስራ ፈጣሪዎች ምቹ የሃብት ማሰባሰቢያ መንገድ ስለመሆኑ እንዲሁም ለኢንቨስተሮች ጥበቃ ያለው የህግና የአሰራር ማእቀፍ ተብራርቷል።
በመድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎች መድረኩ ጠቃሚ እንደነበር በመግለጽ፣ በቀጣይ የካፒታል ገበያን በጥልቀት የሚያስረዳ ተከታታይ እድል እንዲመቻች ፍላጎታቸውን አሳይተዋል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?