የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት ከሀረሪ እና ሶማሌ ክልል እንዲሁም ከድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ለተወጣጡ ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ሌሎች ተሳታፊዎች የሁለተኛ ዙር የስልጠና መድረክ አዘጋጅቷል።ስልጠናውን ላጠናቀቁ 70 ተሳታፊዎች ሰርተፊኬት ተሰጥቷል።
ስልጠናው በዋናነት የዳኞች እና የሕግ ባለሙያዎችን አቅም በማሣደግ በኢትዮጵያ እየተገነባ ያለውን የካፒታል ገበያ ስርዓት ውጤታማ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡
አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ ከሶማሌ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንዲሁም ከሶማሌ ክልል የፍትህ አካላት ባለሙያዎች ማሰልጠኛና የህግ ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን ስምምነቱ የስልጠናውን ተደራሽነት በማስፋት ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስራ ለመስራት የሚያግዝ ነው።

