የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት በተጠናቀው በጀት አመት ውጤታማ ተግባራትን አከናወኗል

የአስተዳደራዊ ፍርድቤቱ የ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 በጀት አመት እቅድ ግምገማ አካሄዷል።
በተጠናቀቀው በጀት አመት ችሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የዲጂታል ፍርድቤት ስርዓት ተዘርግቶ ተከራካሪ ወገኖች ባሉበት ሆነው ክርክራቸውን ማድረግ እና ማስረጃ ማቅረብ እንዲችሉ ተደርጓል።
በተጨማሪም በህግ ባለሙያዎች መካከል ተመሳሳይ የህግ አተረጓጎም እንዲኖር ፍርድቤቱ የሚሰጣቸው ውሳኔዎች ተገማች እንዲሆኑ እና በማስተማሪያ ሰነድነትም የሚያገለግል ጋይድቡክ (Ethiopian Capital Market Guidebook for Judges and Lawyers) ተዘጋጅቶ ይፋ ተደርጓል።
ፍርድቤቱ በበጀት አመቱ በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግብይት ስነ ምህዳር ያለውን ሚናና ኃላፊነት ለመወጣት በአጠቃላይ 18 የስልጠና መድረኮችን በማዘጋጀት 1405 ለሚሆኑ ተሳታፊዎች የመጀመሪያና ሁለተኛ ዙር ስልጠና ተሰጥቷል።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣አማራ፣ሀረሪ፣ሶማሌ ክልል ጠቅላይ ፍርድቤቶች፣ከድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ፍርድቤት እና ሶማሌ ክልል የህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ጋር የካፒታል ገበያ የህግ ማዕቀፍ ስልጠናዎችን በትብብር ለመስጠት የህግና ፍትህ ኢንሰቲትዩት ስርዓተ-ትምህርት አካል ለማድረግ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሞ ወደ ስራ ተገብቷል።
በምስራቅ አፍሪካና በአፍሪካ ውስጥ ከሚገኙ አገራት አቻ የካፒታል ገበያ ፍርድቤቶች ጋር ቀጠናዊ እና አህጉራዊ የካፒታል ገበያ ፍርድቤቶች ፎረምን በትብብር ለማቋቋም የሚያስችል የመነሻ ሃሳብ ለሰባት የአፍሪካ ሀገራት (ታንዛንያ፣ኬንያ፣ ናይጄሪያ፣ኡጋንዳ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሞሪሺየስ ና ዛምቢያ) ተዘጋጅቶ ተልኳል።
በበጀት አመቱ የታየውን ጥንካሬ በቀጣይ በጀት አመት ማስቀጠል እንደሚገባም ሪፖርቱ በቀረበበት ወቅት ተገልጿል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?