የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።
አስተዳደራዊ ፍርድቤቱ በሩብ አመቱ ችሎቱን ዘመናዊና ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ በማደራጀት ማንኛውም የችሎት አገልግሎት ተጠቃሚ የችሎት ሂደቱን ባለበት ሆኖ መከታተል የሚያስችል ስርዓት አጠናቋል።
በተጨማሪም ከፌደራል እና ከኦሮሚያ ክልል ለተውጣጡ 97 የፍትህ ተቋማት ባለሞያዎችና ሃላፊዎች ስለ ካፒታል ገበያ ምንነት እና ተያያዥ ርዕሶች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።
አስተዳደራዊ ፍርድቤቱ በአዲስ ዘመን እና ሪፖርተር ጋዜጣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፅሁፎች በሳምንት አንድ ጊዜ በማሳተም ህበረተሰቡ ስለ ካፒታል ገበያ እና ስለተቋሙ የስራ ሂደት መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል።
በ3 ወራት የቢሮ ኤርጎኖሚክስ ስራዎችም ተጠናቀዋል። በተጨማሪም በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የተቋሙን ሰራተኞች በማሳተፍ በሸገር ዙሪያ ሱሉልታ ክፍለ ከተማ መነ-አብቹ ወረዳ በሁለት ዙር 500 የአፕል፣ ዜቱናና እና ሌሎች አገር በቀል ችግኞችን መትከል ተችሏል።
ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው 25 ሰዎች ሁለት ሁለት የዕርባታ በጎች እና ለ50 ተማሪዎች የአንድ አመት የመማሪያ ቁሳቁሶች ድጋፍ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል።
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት በሩብ አመቱ ከተመደበለት በጀት 90 ነጥብ 4 በመቶ ስራ ላይ ማዋል ተችሏል።
እነዚህ በጠንካራ ጎን የታዩ በመሆኑ በቀጣይ የታየው ጥሩ አፈጻጸም ማስቀጠል ይገባል።
