የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት በሲዳማ ክልል

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት ከሲዳማ ክልል የፍትህ ተቋማት ለተወጣጡ ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ከፍተኛ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እያካሄደ ነው።

አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ በሀዋሳ ከተማ ከሲዲማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ከፍትህ ቢሮ፣ ከስነ ምግባር እና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ፣ከፖሊስ ኮሚሽን እና ከርዕሰ መስተዳደሩ ጽ/ቤት ለተወጣጡ ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ከፍተኛ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅቷል።

የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ ሰብሳቢ ዳኛ አቶ አብነት ዘርፉ: የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ስለ ካፒታል ገበያ ምንነት፣ የካፒታል ገበያ የህግ ማዕቀፎች እና የገበያው ተዋንያን ሃላፊነት እንዲሁም በገበያው ውስጥ የተከለከሉ ተግባራትን እና የሚያስከትሉትን ተጠያቂነት መረዳት ለግብይቱ ስርአቱ ስኬት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ደምሴ ዱለቻ የካፒታል ገበያ በሀገራችን መጀመሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን በማሳለጥ ጉልህ ድርሻ አለው ብለዋል።

አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ ስለ ካፒታል ገበያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማዘጋጀቱ በክልሉ ለሚገኙ የፍትህ ተቋማት ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ከፍተኛ አመራሮች በዘርፉ ያላቸውን ግንዛቤ እንዲያሳድጉ ፋይዳው ከፍተኛ ነው ሲሉ አቶ ደምሴ ተናግረዋል።

በተጨማሪም አስተዳዳራዊ ፍርድ ቤቱ ከሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር በጋራ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ስኬት ተቋማችን ዝግጁ ተገቢውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?