የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የዳኝነት፣ የፍትህና ፋይናንስ ሴክተር ተቋማት ለተወጣጡ ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ስርአት እውን መሆን ዋነኛ ምክንያቶች መካከል የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ስብራቶች ማከሚያ ከሚሆኑ ጉዳዮች እንደ አንዱ መቆጠሩ ነው።
ይህ ስርአት እውን እንዲሆን፣ የሚገነባው የካፒታል ገበያም ውጤታማነት እንዲረጋገጥ፣ ገበያው አስተማማኝ ለኢንቨስትመንት የሚውል ሃብት ምንጭ እንዲሆን፣ እንደዚሁም የኢንቨስተሮች መብት እና ጥቅም ተገቢ ጥበቃ እንዲያገኝ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት መመስረት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተሳተፊዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል።
