የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት በሶማሌ ክልል

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከሶማሌ ክልል የዳኝነት፣ የፍትህና ፋይናንስ ሴክተር ተቋማት ለተወጣጡ ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።
ፍርድ ቤቱ በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ወይም የባለስልጣኑን ስልጣን የሚያስፈጽም ሰው በካፒታል ገበያ አዋጅ፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ሌሎች አግባብነት ያላቸው ህጎች መሰረት የሰጡትን ውሳኔዎች በይግባኝ የመመርመር ስልጣን አለው።

ፍርድ ቤቱ ውሳኔዎቹን ሊያጽና፣ ሊሻር ወይም ሌላ ተገቢ ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል።

የፍርድ ቤቱ ስልጣን በባለስልጣኑና በሰነደ ሙዓለ-ንዋይ ገበያው ወይም ራሱን በራሱ የሚቆጣጠር ድርጅት መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን፣ በባለስልጣኑና በግብይት ተሳታፊዎች መካከል፣ በተሳታፊዎች እርስ በርሳቸው እና ከደንበኞቻቸው/ኢንቨስተሮች ጋር የሚነሱ ጉዳዮችን ያካትታል።

እንዲሁም የምዝገባ ውድቀት፣ የፈቃድ መታገድ ወይም መሰረዝ፣ ከገበያ መዝገብ ማስወገድ እና በካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ወይም በገበያው ድርጊት ምክንያት የገንዘብ ጉዳት የደረሰባቸው ኢንቨስተሮች የካሳ ፈንድ ጥያቄዎችን እንደሚያስተናግድ ተሳተፊዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?