የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት በሀረሪ ክልል እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት ከሀረሪ ክልል እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ስር ከሚገኙ 17 የተለያዩ ተቋማት ለተወጣጡ 88 ተሳታፊዎች የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።

የሐረሪ ክልልና ድሬደዋ ከተማ እያደገ የመጣ የንግድ እንቅስቃሴ ያላቸው በመሆናቸው፣ ባለሀብቶች በካፒታል ገበያው ላይ ዘላቂ እምነት እንዲኖራቸው የአስተዳደራዊ ፍርድቤቱ ድርሻ ከማንኛውም ተቋም የሚበልጥ ነው።

የውይይት መድረኩ የተካሄደበት ወቅት ወቅቱን የጠበቀ እና በሀገራችን እያደገ ያለውን የኢንቨስትመንት ስርዓት በትክክል ለማስተናገድ ከማገዙም በላይ የእርስ በርስ ትውውቅ እና የልምድ ልውውጥ ማድረግ ወሳኝ ነው።

አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ በድሬደዋ ከተማ በመገኘት የተካሄደው የውይይት መድረክ ስለ ካፒታል ገበያ አዋጅ ያለውን ግንዛቤ አይን ገላጭ እንዲሆን በማሰብ የተዘጋጀ ሲሆን በቀጣይም የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ፣ መመሪያዎችን እና አሰራር ስርዓቱን በተመለከተ የተለያዩ ሀገራት አለም አቀፍ ተሞክሮ እና በተግባር ልምምድ ማድረግን ያካተተ ሰፊ መድረክ ይዘጋጃል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?