የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፍትህና ፋይናንስ ሴክተር ተቋማት ለተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳኞች እና አቃቢያነ ህግ ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ኢንቨስተሮች ጥበቃ ለማድረግ በክልሉ የሚገኙ ተቋማት ስለ ካፒታል ገበያ ምንነት፣ የካፒታል ገበያ የህግ ማዕቀፎች እና የአሰራር ስርዓትን በተመለከተ ግንዛቤን ማላቅ የውይይት መድረኩ አላማ ነው።

በተለይም ከካፒታል ገበያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ብቻ በይግባኝ የሚመለከት ልዩ ፍርድቤት ስራ መጀመሩን በማስተዋወቅ በጋራ ለሚሰሩ ስራዎች ዝግጁነት እንዲኖር የሚያስችል ነው። አስተዳደራዊ ፍርድ ቤቱ በቀጣይ ለፍትህ ተቋማት ብቻ የሚሆን ጥልቀት ያለው ስልጠና በቅርቡ ይጀምራል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?