የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድቤት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዳኝነት፣ የፍትህና ፋይናንስ ሴክተር ተቋማት ለተወጣጡ ዳኞች፣ አቃቢያነ ህግ እና ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው።

አስተዳደራዊ ፍርድቤቱ የውይይት መድረክ ያዘጋጀበት ዋና አላማ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ ተቋማት ጋር ወደፊት ለሚያከናውናቸው ስራዎች የትውውቅ እና የዘርፉን ምንነት በተመለከተ ግንዛቤ የሚፈጥር ነው።

በተለይም የአስተዳዳራዊ ፍርድቤቱ መቋቋም የገበያ ታማኝነትን የሚያጠናክር፣የኢንቨስተሮችን አመኔታ የሚያጎለብት እና የካፒታል ገበያ አለመግባባቶችን ለመፍታት ፍትሃዊ፣ግልጽ እና ቀልጣፋ አሰራርን የሚከተል ነው።

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ወይም የባለስልጣኑን ተግባርና ስልጣን በሚያስፈጽም ሰው በተላለፉ ውሳኔዎች ላይ የሚቀርቡ ይግባኞችን መርምሮ የሚወስን ከመደበኛው ፍርድቤት የተለየ ተቋም መሆኑን ተሳተፊዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ተደርጓል።

Newsletter Updates

Subscribe to receive the latest announcements, regulatory updates, and news from ECMAT

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት

በካፒታል ገበያ ሥነ-ምህዳር አፍሪካዊ የፍትህ ተምሳሌት መሆን

መገኛችን

አራዳ ክፍለ ከተማ ፣ ፒያሳ ዋስትና ህንፃ 16ኛ ፎቅ ፣ አዲስ አበባ ፥ ኢትዮጵያ

+251111278823

admin@ecmat.gov.et

Follow Us

💬
ECMAT Digital Assistant
Welcome to the Ethiopian Capital Market Administrative Tribunal. How can I assist you with tribunal procedures or dispute resolution today?